Current Articles | Categories | Search | Syndication
የኢትዮጵያን ሚሌኔዬም በተለያየ መልክ አክብረናል፤ ይህንን ታሪካዊ ቀን ከዛሬ 2000 ዓመት በፊትና በኋላ ከነበረዉ የአገራችን ታሪክ ጋር በማገናዘብ እንዲሁም ህያዉ ከሆነዉ ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ ጋር እንዴት እንደተያያዘ በመጥቀስና ተጨባጭ የሆኑ ታሪካዊ ማስረጃዎችን በመጠቆም በቶሮንቶ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን ፓስተሮች አንዱ የሆኑት ፓስተር ኤፍሬም ላዕከማርያም የሚከተለዉን መልዕክት አቅርበዉልናል፡፡
ባደግንበት ባሕል ክልል ተወስነን ለምንኖረውም ሆነ የባህሉን ድንበርን ክልል አልፈን፣ በረሃውን አቋርጠን፣ ባሕሩን ተሻግረን ለምንኖረው ሁሉ ይህን አባባል በተመለከተ ለማሰተላለፍ የምንፈልገው መልእክት አለን። አማኞች በትዳራቸው...
በብዙዎች ከቀድሞ ጀምሮ ያለዉ ጥያቄ የጌታ ዳግም መምጣት ሲሆን ከመጽሐፍ ቅዱስ በመጥቀስ አንዳንዶች ጌታ አሁን ይመጣል (2ኛ ተሰ. ምዕ 2 ና 3) ያሉ እንደ ነብሩ እንዲሁም ደግሞ በ2ኛ ጴጥ. ምዕ 3 ላይ አለም ከተፈጠረ ጀምሮ ሁሉ ነገር እንዳለ ነዉ ምንድነዉ የምትሉት ያሉና የሚሉ እንዳሉ እናያለን። ለዚህ ጥያቄ መልስ በቂ ምላሽ የሚሆን በ 5/18/08 እሁድ ፕሮግራም በፓስተር ኤፍሬም ላዕከማርያም የቀረበዉን መልእክት ክፍል አንድ እንደሚክተለዉ እናቀርብላችኋለን።
ባለንበት ዘመን በመላው የአለም ሕብረተስብ ስዉንና ቤተስቡን የሚያናውጡ ጉልህ የሆኑ የቤተስብ ችግሮች እንዳሉ ግልጽ ነው። በተለይም እኛ በውጭ አገር የምንገኝ ከኢትዮጵያ ህብረተስብ ሀገራችንን የተውንበት በመገፋት እንዲሁም በተለያዩ ምክንያቶችም ናቸው፤ አሁንም በመጻተኛነት በዚህ በምንኖርበት...
ያለ መንፈስ ቅዱስ ሰው ከንቱ ነው፣ ጠማማ መንገድንም ይከተላል፤ ያለ መንፈስ ቅዱስ ምሪት ሕይወት፣ ኑሮ፣ አገልግሎት ሁሉ ድካም ብቻ ይሆናል። ዳዊት ራሱ በቍ. 4 ላይ "ነፍሴ በውስጤ አለቀችብኝ" ሲል እንመለከታለን።
ጌታን ከማወቃችን በፊት በበደላችንና በኃጢአታችን ምክንያት መንፈሳችን ሙት ነበር (ኤፌሶን 2፣1)። ጌታን ካገኘን በኋላ ግን የእግዚአብሔር መንፈስ ወደ ውስጣችን ገብቶ አዲስ ሕይወትን ሰጠን፣ በመንፈስም ሕያዋን ሆንን (ሮሜ 8፣10-11)፤ ያን ጊዜ መንፈሳዊ ዓይናችን ተከፈተ፣ ያኔም ማን መሆናችን ብቻ ሳይሆን የማን መሆናችንን ተረዳን።
"ለበረከትም ሁን! You Shall Be a Blessing!"
በ1998 ዓ.ም. ግንቦት ወር ውስጥ Rev. Ruddy Wiebe ከተባሉት የመጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጅ ፕሪንሲፓልና ሌሎች 6 ከተለያዩ አገሮች የመጡ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች ጋር ፔንሲልቫንያና ኒውዮርክ ለአንድ ሳምንት በመዘዋወር በተለያዩ የአሜሪካ አብያተ ክርስቲያን የማገልገልና የመገልገል ዕድል ገጥሞን ነበር።
George Whitefield was born on December 16, 1714, in the Bell Inn, Gloucester, England. His father died when George was two, and his widowed mother; Elizabeth struggled to raise him up.